Lej_solomon

Lej_solomon

46p

18 comments posted · 30 followers · following 0

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - ጠቅላይ ሚኒስ... · 0 replies · +4 points

ይፋጃል ወገን የመታሀው ምስማር ባለ 12 ቁጥሩን ነው ብል የሚሻል ይመስላል። ለምን ቢባል በበቂ ሁኔታ እንደገለፅከው ናፖሊዮን ሁሌም ልክ ነው የሚሉ የዘመኑ Grande Armée ከሰማይ በታች መለስ ሁሌም ልክ ነው የሚሉበት ዘመን አብቅቶ ከእውነት ጋር መታረቅ መፈለጋቸው መዳኛ ጥግ እያፈላለጉ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው። ጨው ለራስሽ ስትዪ ጠፍጪ አሊያም ድንጋይ ብለው ይወረውሩሻል እንደሚባለው ንስሀው ከሁሉ በፊት ለራስ ነው።

ብራሾ ይፋጃል

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - ሰንሻይን ኮን... · 1 reply · +2 points

በበርካታ አገራት አንደ ሰንሻይን የመሳሰሉ ታላላቅ ሪል ስቴቶች ባላቸው ሰፊ አቅም የሀገራቸውን የመኖሪያቤት እጥረት እና የዋጋ ንረት ለመገደብ ሲሰሩ ይታያሉ ሰንሻይን ግን በዚህ ዜና እንደምንረዳው በዋንኛነት ትርፍን የማጋባስ ኣላማ ዋንኛው መሰረቱ በመሆኑ 400000000 አራት መቶ ሚሊዮን በሚፈጅ ወጭ የገነባውን 210 ሁለትመቶ አስር ቤቶች ለያንዳንዳቸው በአማካይ 2000000 ሁለት ሚሊዮን በፈጀ ወጪ ገንብቶ ከእጥፍ በላይ ትርፍ በሚያስገኝ መንገድ እስከ 4000000 አራት ሚሊዮን እና ከዚያም በላይ ሲቸበችባቸው እናያለን ይህም የሀገሪቱን የመኖሪያ ዋጋ ከማረጋጋት ይልቅ በይበልጥ ሲያባብሰው ይታያል። ለመሆኑ የዚህ አይነቱ አሰራር ማብቂያው መቼ ይሆን

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - ሰበር ሰሚ ች... · 0 replies · +1 points

የሚደንቀው የፍርድቤቱ ውሳኔ ሳይሆን የተከሳሾቹ ፍጹም መልአክት መሆናቸው ነው።በአገራችን ንጉስ አይከሰስ ሰማይ አይታረስ አንደሚባለው ወያኔን መክሰስ አይቻልም ብሎ መደምደም የሚቀል ነበር።በአንድ ጉዳይ እንኩዋን ወያኔ ሲረታ የማይታየው እውነት ከወደ ትከሻቸው ትንንሽ ክንፍ ያበቀሉ ፃድቃን ሆነው ይሆን-እንደው እውነት የፍትህ ስርእት በእገሪቱ ካለ ለህሊናው ፍርድ የሚሰጥበት ጊዜ ይድርስ ይሆን-የሚያሳዝን ነው።ነገም ሌላ ቀን ነውና ይህ ሁሉ አሳዛኝ ሁኔታ አልፎ በህዝብ ላይ ይህንን በደልና ግፍ የሚጭኑ ሁሉ በሰፈሩበት ቁና የሚሰፈሩበት ጊዜ ይደርስ ይሆናል አስከዚያው ቅሎች ድንጋይ እየሰበሩ መግፋታቸው የግድ ሆኖአል።

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - ምርጫ ቦርድ ... · 0 replies · +1 points

ታጋይ መርጋ የዘነጉት ነገር ቢኖር የአውሮፓ ህብረት ታዛቢዎች ቀደምሲል የተፈራረሙት ከውጭ ጉዳይ ጋር እንጂ ከምርጫ ቦርድ ተብዬው ጋር አይደለም። ታዲያ በምን መንደርደሪያ ነው መርጋ ህብረቱን ለመተቸት የበቁት- በቅድሚያ የስምምነቱን መነሻ እና መዳረሻ አብረው በወያኔ ድርጅታዊ ስራ ውስጥ ተሳትፈውበታልና ዝርዝሩን ማወቃቸውን ለመግለፅ ከሆነ ይሄ ሊያስማማ ይችላል።ካልሆነ ግን አቀራረባቸው የሚያሳፍር ብቻ ሳይሆን የሚያስንቅም ጭምር ነው።ወያኔ በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ማንኛውንም እንቅስቃሴ በቁጥጥሩ ውስጥ ማዋሉን በፉከራ በሚገልፅበት በአሁኑ ወቅት የሚታይ ጭስ ሁሉ ቢያስበረግገው የሚደንቅ አይደለም ለምን ቢሉ የአበሩን ጠባሳ ያየ በእሳት አይጫወትም ነውና።

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - መኢአድ ለክል... · 0 replies · -1 points

ጀግናው.--- ጀግንነት በምን እንደሚለካ ማወቁ በስሙ እንደ መፎከር የቀለለ አይደለም ። በርግጥ ዘመኑ በርካታ የሚያላግጠ- ጀግኖች ያየንበት በመሆኑ ያንተው ሳቅ አይደንቅም። ጀግናው- ወያኔ ከከፋው አምባገነናዊ ባህሬው በተጨማሪ ስር የሰደደ ይልኙታቢስ መሆኑን ጭምር የምትስተው አይመስለኝም ።ይልኙታ ሀገራዊ የሆነ መለያ ቅርሳችን የሆነው እንደ ኢትዮጵያዊ በአንድ ውቅት ከሰራነው ስህተት የምንማር መሆናችንን ስለሚያመሳክርልን ነበር።ሆኖም ወያኔ ግን ይህንን የመሰለ አገራዊ መገለጫ የሆነውን ይሉኝታ አልፈጠረበትምና ደጋግሞ ለሚሰራው ስህተትና ወንጀል መለስ ብሎ ለማሰብ የሚቻለው አይደለም።ለዚህም ነው ወያኔን ከርሞ ጥጃ ነው ማለት የሚቀለው።ጥላቻን፥ንቀትን፥ክህደትን እና ጭቃኔን መርሁ ላደረገ እንደወያኔ ካለ ሀይል በርግጥ ይሉኝታን መጠበቅ የዋህነት ነው። እናም ወያኔ ሐሰትን በድራማ ተውኔት እሽሞንሙኖ ባቀረበ ቁጥር የሚሞኝ የዋህ ዛሬ የሚገኝ አይመስለኝም።እናም ያለው አማራጭ ዛሬ አንድ እና አንድ ነው ይሀውም ወያኔ ከገባበት ማጥ በራሱ ሀይል መውጠት መቻል ብቻ።ያኔ አንተም ወንድሜ እውነተኛውን ሳቅ መሳቅ ይቻልሀል ብዬ አምናለው።
ቸር ሰንብት

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - "እኛ ያለን ኩ... · 0 replies · -3 points

ዶክተር አሸብር በምርጫ ሳይሆን በማሙያ መልክ ወያኔ እድሉን የከፈተላቸው ተወዳዳሪ ቢባሉ የሚቀል ይሆናል።ለምን ቢባል ወያኔ ያልፈለገውን ግለሰብ ለማስወገድ ግምገማ ሳያስፈልገው ስራውን እሳቸው የፈጸሙለት በመሆኑ።ግለሰቡ እንደ አንድ ተወዳዳሪ ይህ ነው የሚባል የመወዳዳሪያ አጀንዳ ሳይዙ እንደው በደመነፍሰ ያልወደዱትን ለማግለል ብቻመንቀሳቀሳቸውን የተከታተል ሁሉ የሚረዳው ቁምነገር ቢኖር በሁሉም መስክ ምርጫው ምን ያህል የዘቀጠ እና እንደ ግለሰብ የጠላኽውን ግለሰብ እንደ ፓርቲ ደግሞ ያልወደድከውን ፓርቲ የህዝብ ጠላት አድርጎ በማቅረብ ሕዝብን ከሕዝብ ጋር ለማቃራን በተለይ ወያኔ ሁነኛ ስራ በመስራት የተሳካለት መሆኑን የተገነዘብንበት ነው።ወያኔ ባለፉት19 አመታት ወስጥ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከፋፍሎ ለመምታት የቻለብትን የተሳካ ስራ የሰራበት ወቅት ቢኖር አሁን የምንገኝበት ጊዜ ነው ቢባል የሳተ እየደለም።ይህም በቀጥታ በድርጅቱና እንደ አሸብር በተዘዋዋሪ ያሰለፋቸው ሃይሎች ያገኙትን አምባገነናዊ እድል መመልከት ይቻላል።እናም ከዚህ የምንማረው አገራችን ኢትዮጵያ የገባችበትን ማጥና በሕዝቡ ሉአላዊነት ላይ ያጠላውን አደጋ ነው።

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - የጠቅላይ ፍር... · 1 reply · +2 points

ትንሽ ቀልድ ለአቶ መንበረ የምትመች ቅቅቅቅቅቅ
ሟችነፍሱ ሰማይ ቤት እንደደረሰ የሰማይ ቤት ዳኞች ገሃነም ወይም ገነት ለመግባት ሁለቱንም ስፍራዎች ጎብኝቶ መምረጥ እንዳለበት ይነግሩታል፡፡ በመርሐ-ግብሩ መሰረትም በመጀመሪያ ገሃነምን እንዲጎበኝ ይጋበዝና ገና ከበሩ ላይበመልካም አለባበስ የተሸቆጠቆጠው ሳጥናኤል በሞቀ ሰላምታ ተቀብሎት ወደ ውስጥ ይዞት ይገባል፡፡
ገሃነም ውስጥ የሟች የድሮ ወዳጆች ሁሉ ተሰብስበው እየጠጡ፣ ከረንቦላ እየተጫወቱ፣ በሙዚቃ እየጨፈሩ አስደሳች ጊዜ ሲያሳልፉ ተመለከተ፡፡ ከዚያም ወደ ገነት ተወሰደ፡፡ ገነት እንደገባ አንድም የድሮ ጓደኛውን ሊያገኝ አልቻለም:: ከዚያም በላይ ሲያስበው ያስመረረው ግን በገነት ያሉ ሰዎች ስራቸው ሁሉ ነጫጭ ለብሰው ማሸብሸብ፣ መጸለይና መስገድ ብቻ መሆኑ ነው ፡፡ ሟች ሁለቱንም ሁኔታዎች አመዛዝኖ ሲያበቃ ገሃነም ከወዳጆቹ ጋር ለመቀላቀል ወስኖ ፊርማውን አኖረ፡፡ በማግስቱ ወደገሃነም ሲወሰድ ግን የጠበቀው ነገር ሌላ ነበር፡፡ ሳጥናኤል በአስፈሪ እርቃኑ ቆሞ እህል-ውሃ የማያሰኝ ጅራፍ ይዞ እየዠለጠ ወደ ውስጥ አስገባው፡፡ ውስጥ የነበሩት ጓደኞቹም ግማሽ ሰውነታቸው በእሳት ተዘፍቆ ሲሰቃዩ ተመለከተ፡፡ ወዳንድ ጓደኛው ጠጋ አለና ትላንትና ያየሁት ሕይወት የት ሄደ? ብሎ ቢጠይቀው፡፡ አይ እሱማ የምርጫ ቅስቀሳ ነው ብሎት እርፍ አለ፡፡

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - "ከሊበራል ዴ... · 0 replies · +1 points

ወንድም ፍቅሩ እንደው ከርሞ ጥጃ ብልህ ይሻል ይሆን--ስለአቶ ልደቱ የፖለቲካ ሞት መሞት ከዚህ የተሻለ ምን ማስረገጫ ያስፈልጋል፥በከተማም በገጠርም የሚገኝ ሕዝብ አንቅሮ ሲተፋው እያየህ-ይህ የህዝብ-ውሳኔ ልደቱ በተከታታይ በሕዝብ ላይ ለሰራው በደል የተሰጠው ምላሽ እኮ ነው።ልደቱ በሕዝቡ ውስጥ ያለውን ጥያቄ አሳንሶ የሶሰተኛ መንገድ ደቀ-መዝመርነት ሲያምረው አኮ ነው ሕዝብ በቃሀኝ ያለው።ወያኔ ከተያያዘው አረመኔዊው ተግባሩ ኢምንት ፈቅ ሳይል የሱ ከወዲህ ወዲያ መላጋት ምን ለመጨበጥ ሲባል ነበር--እናም የሕዝብ ጥያቄ ሆነው የቀጠሉትን በሱ መንሸራረት ማስቀረት የሚቻል ያለመሆኑን መረዳት ቢገባው የተሻለ ነበር። ልደቱ ዛሬ በመግለጫ ጋጋታ ሕዝብን እያራከሰ እና አያዋረደ መቀጠሉ ለፓለቲካ ሞት መሞቱ አይነተኛ መግለጫው እኮ ነው አሊያማ ሕዝቡ በአሁኑ ወቅት የሱን ዲስኩር የሚያዳምጥበት ትእግስቱ ማለቁን ከእርሱ በላይ ማን አውቆት--እናም ልደቱ አገራችን በፓለቲካው መስክ ካፈራቻቸውና በአሳፋሪ ተግባራቸው ህዝብ በታሪክ ሲያስታውሳቸው ከሚኖሩት ውስጥ ዋናውን ስፍራ የሚይዝ ነው። ስለዚህ አቶ ልደቱን አሁን የሚያስፈልጋቸው የፖለቲካ ነፍሳቸውን እግዜሃብሄር ይማረው ማለት ብቻ ነው። የሚማር ባይሆንም።

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - "ከሊበራል ዴ... · 2 replies · +1 points

ሪፖርተር ለአቶ ልደቱ ያቀረባቸው ጥያቄዎች ተገቢ የሚባሉትን ነው። ነገርግን ከነዚህ ጥያቄዎች በተጨማሪ አቶ ልደቱ በተጨማሪ ቢመልሱት የሚገባው ጥያቄ ቢኖር፧ ወደ ቡግና ለምርጫ ከማቅናታቸው በፊት ወያኔ ከከተሞች አካባቢ ይልቅ በገጠር ወረዳዎች በሕዝቡ ላይ የሚያሳርፈውን ከፍተኛ አፈናና ጫና እንዳለና ይህንንም ቀደም ሲል በተደረጉ ምርጫዎች በሚገባ የሚያውቁት መሆኑን ከዚህም በተጨማሪ በተለይ የውጭ ታዛቢዎች በቅርብ በገጠር ወረዳዎች ተገኝተው ለመከታተል አለመቻላቸው፧እንዲሁም ሕዝቡ ብሶቱንና በደሉን የሚያስተጋባበት እድል በገጠሩ ከከተማው ይባስ የከፋ መሆኑን እየተረዱ ገጠሩን የመረጠ-ት ምን ያህል በከተማው ሕዝብ ተስፋ ቢቆርጠ- ነው የሚል ነበር
ለነገሩ አቶ ልደቱ የፖለቲካውን ሞት አልሞት ማለታቸው እንጂ ሕዝቡ በከተማም ይሁን በገጠሩ አንቅሮ ከተፋቸው ሰነበተ።

13 years ago @ Reporter - Amharic Ver... - ኢዴፓ ለመድረ... · 0 replies · +1 points

ወንድሜ ያሲን እውቀት ረከስ ይሉሀል ይሄ ነው ።